Header Include

Amharic translation - Africa Academy

Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy

QR Code https://quran.islamcontent.com/aa/amharic_zain

وَٱلنَّجۡمِ إِذَا هَوَىٰ

1. በኮከብ እምላለሁ በገባ ጊዜ፤

1. በኮከብ እምላለሁ በገባ ጊዜ፤

مَا ضَلَّ صَاحِبُكُمۡ وَمَا غَوَىٰ

2. (እናንተ የመካ ሰዎች ሆይ)፤ ባልደረባችሁ ሙሐመድ ከሐቅ አልተሳሳተም። አላፈነገጠም።

2. (እናንተ የመካ ሰዎች ሆይ)፤ ባልደረባችሁ ሙሐመድ ከሐቅ አልተሳሳተም። አላፈነገጠም።

وَمَا يَنطِقُ عَنِ ٱلۡهَوَىٰٓ

3. ከልብ ወለድ ስሜቱም አይናገርም::

3. ከልብ ወለድ ስሜቱም አይናገርም::

إِنۡ هُوَ إِلَّا وَحۡيٞ يُوحَىٰ

4. እርሱ (ንግግሩ) ከአላህ የተወረደ እንጂ ሌላ አይደለም።

4. እርሱ (ንግግሩ) ከአላህ የተወረደ እንጂ ሌላ አይደለም።

عَلَّمَهُۥ شَدِيدُ ٱلۡقُوَىٰ

5. ሀይለ ብርቱ የሆነው አስተማረው::

5. ሀይለ ብርቱ የሆነው አስተማረው::

ذُو مِرَّةٖ فَٱسۡتَوَىٰ

6. የእውቀት ባለቤት የሆነው:: ከዚያም ላይ ሆኖ ተመቻቸ።

6. የእውቀት ባለቤት የሆነው:: ከዚያም ላይ ሆኖ ተመቻቸ።

وَهُوَ بِٱلۡأُفُقِ ٱلۡأَعۡلَىٰ

7. በላይኛው አድማስ ላይ ሆኖ፤

7. በላይኛው አድማስ ላይ ሆኖ፤

ثُمَّ دَنَا فَتَدَلَّىٰ

8. ከዚያም (ነቢዩን) ቀረበው፤ በጣም ተጠጋውም።

8. ከዚያም (ነቢዩን) ቀረበው፤ በጣም ተጠጋውም።

فَكَانَ قَابَ قَوۡسَيۡنِ أَوۡ أَدۡنَىٰ

9. ከዚያም የሁለት ደጋን ጫፎች ያህል ወይም ከዚያም ባነሰ ርቀት ላይ ሆነም::

9. ከዚያም የሁለት ደጋን ጫፎች ያህል ወይም ከዚያም ባነሰ ርቀት ላይ ሆነም::

فَأَوۡحَىٰٓ إِلَىٰ عَبۡدِهِۦ مَآ أَوۡحَىٰ

10. እናም (አላህ) ለአገልጋዩ (ለሙሐመድ) ማውረድ የሻውን አወረደ::

10. እናም (አላህ) ለአገልጋዩ (ለሙሐመድ) ማውረድ የሻውን አወረደ::

مَا كَذَبَ ٱلۡفُؤَادُ مَا رَأَىٰٓ

11. ያየውን ነገር ሁሉ ልቦናው አላስተባበለዉም::

11. ያየውን ነገር ሁሉ ልቦናው አላስተባበለዉም::

أَفَتُمَٰرُونَهُۥ عَلَىٰ مَا يَرَىٰ

12. ታዲያ (ከሓዲያን ሆይ!) በሚያየው ጉዳይ ላይ ትከራከሩታላችሁን?

12. ታዲያ (ከሓዲያን ሆይ!) በሚያየው ጉዳይ ላይ ትከራከሩታላችሁን?

وَلَقَدۡ رَءَاهُ نَزۡلَةً أُخۡرَىٰ

13. እርግጥ በሌላይቱም መውረድ (ነቢዩ ሙሐመድ መልዐኩ ጂብሪልን) አይቶታል::

13. እርግጥ በሌላይቱም መውረድ (ነቢዩ ሙሐመድ መልዐኩ ጂብሪልን) አይቶታል::

عِندَ سِدۡرَةِ ٱلۡمُنتَهَىٰ

14. ይኸዉም ሲድረቱ አል-ሙንተሃ (የመጨረሻቱ ቁርቁራ) በተባለው ዓለም ላይ ነው::

14. ይኸዉም ሲድረቱ አል-ሙንተሃ (የመጨረሻቱ ቁርቁራ) በተባለው ዓለም ላይ ነው::

عِندَهَا جَنَّةُ ٱلۡمَأۡوَىٰٓ

15. እርሷ ዘንድ መኖርያ የሆነችው ገነት አለች::

15. እርሷ ዘንድ መኖርያ የሆነችው ገነት አለች::

إِذۡ يَغۡشَى ٱلسِّدۡرَةَ مَا يَغۡشَىٰ

16. (ቁርቁራይቱን) ሸፋኝ ነገር በሸፈናት ጊዜ (አየው)።

16. (ቁርቁራይቱን) ሸፋኝ ነገር በሸፈናት ጊዜ (አየው)።

مَا زَاغَ ٱلۡبَصَرُ وَمَا طَغَىٰ

17. አይኑ አልተዘነበለም:: ወሰንም አላለፈም።

17. አይኑ አልተዘነበለም:: ወሰንም አላለፈም።

لَقَدۡ رَأَىٰ مِنۡ ءَايَٰتِ رَبِّهِ ٱلۡكُبۡرَىٰٓ

18. ከጌታው ታላላቅ ተዐምራት በእርግጥ ተመለከተ።

18. ከጌታው ታላላቅ ተዐምራት በእርግጥ ተመለከተ።

أَفَرَءَيۡتُمُ ٱللَّٰتَ وَٱلۡعُزَّىٰ

19. (ቁርይሾች ሆይ!) ላትንና ዑዛን አያችሁን?

19. (ቁርይሾች ሆይ!) ላትንና ዑዛን አያችሁን?

وَمَنَوٰةَ ٱلثَّالِثَةَ ٱلۡأُخۡرَىٰٓ

20. ስለ ሶስተኛዋ መናትም የምታውቁትን እስቲ ንገሩኝ::

20. ስለ ሶስተኛዋ መናትም የምታውቁትን እስቲ ንገሩኝ::

أَلَكُمُ ٱلذَّكَرُ وَلَهُ ٱلۡأُنثَىٰ

21. ለእናንተ ወንድ ወንድ ለእሱ ግን ሴት ሴት ታደርጋላችሁን::

21. ለእናንተ ወንድ ወንድ ለእሱ ግን ሴት ሴት ታደርጋላችሁን::

تِلۡكَ إِذٗا قِسۡمَةٞ ضِيزَىٰٓ

22. ይህ ተግባር አድሏዊ ክፍፍል ነው::

22. ይህ ተግባር አድሏዊ ክፍፍል ነው::

إِنۡ هِيَ إِلَّآ أَسۡمَآءٞ سَمَّيۡتُمُوهَآ أَنتُمۡ وَءَابَآؤُكُم مَّآ أَنزَلَ ٱللَّهُ بِهَا مِن سُلۡطَٰنٍۚ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا ٱلظَّنَّ وَمَا تَهۡوَى ٱلۡأَنفُسُۖ وَلَقَدۡ جَآءَهُم مِّن رَّبِّهِمُ ٱلۡهُدَىٰٓ

23. እነዚያ ጣዖታት እናንተና አባቶቻችሁ የሰየማችኋቸው ስሞች ብቻ እንጂ ሌላ አይደሉም::አላህ በእርሷ (መገዛት) ምንም ማስረጃ አላወረደም፡፡ ጣኡት አምላኪዎች ሁሉ ከጌታቸው የተላከላቸው ቅኑ መመሪያ እያለ የሚከተሉት ግን ጥርጣሬንና ስሜትን ብቻ ነው::

23. እነዚያ ጣዖታት እናንተና አባቶቻችሁ የሰየማችኋቸው ስሞች ብቻ እንጂ ሌላ አይደሉም::አላህ በእርሷ (መገዛት) ምንም ማስረጃ አላወረደም፡፡ ጣኡት አምላኪዎች ሁሉ ከጌታቸው የተላከላቸው ቅኑ መመሪያ እያለ የሚከተሉት ግን ጥርጣሬንና ስሜትን ብቻ ነው::

أَمۡ لِلۡإِنسَٰنِ مَا تَمَنَّىٰ

24. የሰው ልጅ የፈለገውን ሁሉ ያገኛልን?

24. የሰው ልጅ የፈለገውን ሁሉ ያገኛልን?

فَلِلَّهِ ٱلۡأٓخِرَةُ وَٱلۡأُولَىٰ

25. መጪውን ዓለምም ሆነ የመጀመሪያው ዓለም የአላህ ብቻ ነው::

25. መጪውን ዓለምም ሆነ የመጀመሪያው ዓለም የአላህ ብቻ ነው::

۞ وَكَم مِّن مَّلَكٖ فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ لَا تُغۡنِي شَفَٰعَتُهُمۡ شَيۡـًٔا إِلَّا مِنۢ بَعۡدِ أَن يَأۡذَنَ ٱللَّهُ لِمَن يَشَآءُ وَيَرۡضَىٰٓ

26. በሰማያት ውስጥ ካሉ መላዕክት አላህ የሚሻውንና የሚወደውን ለሰው ያማልዱ ዘንድ ከፈቀደላቸው በኋላ እንጂ ምልጃቸው የማይፈይድ አያሌዎች ናቸው::

26. በሰማያት ውስጥ ካሉ መላዕክት አላህ የሚሻውንና የሚወደውን ለሰው ያማልዱ ዘንድ ከፈቀደላቸው በኋላ እንጂ ምልጃቸው የማይፈይድ አያሌዎች ናቸው::

إِنَّ ٱلَّذِينَ لَا يُؤۡمِنُونَ بِٱلۡأٓخِرَةِ لَيُسَمُّونَ ٱلۡمَلَٰٓئِكَةَ تَسۡمِيَةَ ٱلۡأُنثَىٰ

27. እነዚያ በመጪው ዓለም የማያምኑት መላዕክትን በእንስት ስም ይሰይማሉ::

27. እነዚያ በመጪው ዓለም የማያምኑት መላዕክትን በእንስት ስም ይሰይማሉ::

وَمَا لَهُم بِهِۦ مِنۡ عِلۡمٍۖ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا ٱلظَّنَّۖ وَإِنَّ ٱلظَّنَّ لَا يُغۡنِي مِنَ ٱلۡحَقِّ شَيۡـٔٗا

28. ለእነርሱም በእርሱ እውቀት የላቸውም። እነርሱ የሚከተሉት ጥርጣሬን ብቻ ነው:: ጥርጣሬ ደግሞ ሀቅን አይተካም::

28. ለእነርሱም በእርሱ እውቀት የላቸውም። እነርሱ የሚከተሉት ጥርጣሬን ብቻ ነው:: ጥርጣሬ ደግሞ ሀቅን አይተካም::

فَأَعۡرِضۡ عَن مَّن تَوَلَّىٰ عَن ذِكۡرِنَا وَلَمۡ يُرِدۡ إِلَّا ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا

29. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከቁርኣን አፈንግጦና የዚችን ዓለም ኑሮ እንጂ ሌላ ከማይመኝ ሰው እራስህን አሽሽ::

29. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከቁርኣን አፈንግጦና የዚችን ዓለም ኑሮ እንጂ ሌላ ከማይመኝ ሰው እራስህን አሽሽ::

ذَٰلِكَ مَبۡلَغُهُم مِّنَ ٱلۡعِلۡمِۚ إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِۦ وَهُوَ أَعۡلَمُ بِمَنِ ٱهۡتَدَىٰ

30. ይህ የእውቀታቸው ጣሪያ (መጨረሻ) ነው:: ጌታህ ግን መንገዱን የሳተውን ሁሉ አዋቂ ነው:: የተቀናውንም እንዲሁ አዋቂ ነው።

30. ይህ የእውቀታቸው ጣሪያ (መጨረሻ) ነው:: ጌታህ ግን መንገዱን የሳተውን ሁሉ አዋቂ ነው:: የተቀናውንም እንዲሁ አዋቂ ነው።

وَلِلَّهِ مَا فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِي ٱلۡأَرۡضِ لِيَجۡزِيَ ٱلَّذِينَ أَسَٰٓـُٔواْ بِمَا عَمِلُواْ وَيَجۡزِيَ ٱلَّذِينَ أَحۡسَنُواْ بِٱلۡحُسۡنَى

31. በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለው ሁሉ የአላህ ነው:: እነዚያን ያጠፉትን በተግባራቸው ለመመንዳትና እነዚያን መልካም የሰሩትንም በመልካሟ (በገነት) ሊመነዳ ነው::

31. በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለው ሁሉ የአላህ ነው:: እነዚያን ያጠፉትን በተግባራቸው ለመመንዳትና እነዚያን መልካም የሰሩትንም በመልካሟ (በገነት) ሊመነዳ ነው::

ٱلَّذِينَ يَجۡتَنِبُونَ كَبَٰٓئِرَ ٱلۡإِثۡمِ وَٱلۡفَوَٰحِشَ إِلَّا ٱللَّمَمَۚ إِنَّ رَبَّكَ وَٰسِعُ ٱلۡمَغۡفِرَةِۚ هُوَ أَعۡلَمُ بِكُمۡ إِذۡ أَنشَأَكُم مِّنَ ٱلۡأَرۡضِ وَإِذۡ أَنتُمۡ أَجِنَّةٞ فِي بُطُونِ أُمَّهَٰتِكُمۡۖ فَلَا تُزَكُّوٓاْ أَنفُسَكُمۡۖ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَنِ ٱتَّقَىٰٓ

32. እነርሱም ከጥቃቅን ጥፋቶች በቀር ከባባድ ወንጀሎችንና አጸያፊ ተግባሮችን የራቁ ናቸው:: ጌታህ ምህረተ ሰፊ ነው:: እርሱ ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜም ሆነ በእናቶቻችሁ ማሕጸን ውስጥ ጽንሶች በሁናችሁበት ጊዜ ያውቃችኋል:: ስለዚህ እራሳችሁን አታሞግሱ:: እርሱ በትክክል የሚፈራውን ሰው ከሁሉም ይበልጥ አዋቂ ነው::

32. እነርሱም ከጥቃቅን ጥፋቶች በቀር ከባባድ ወንጀሎችንና አጸያፊ ተግባሮችን የራቁ ናቸው:: ጌታህ ምህረተ ሰፊ ነው:: እርሱ ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜም ሆነ በእናቶቻችሁ ማሕጸን ውስጥ ጽንሶች በሁናችሁበት ጊዜ ያውቃችኋል:: ስለዚህ እራሳችሁን አታሞግሱ:: እርሱ በትክክል የሚፈራውን ሰው ከሁሉም ይበልጥ አዋቂ ነው::

أَفَرَءَيۡتَ ٱلَّذِي تَوَلَّىٰ

33. ያን ከእምነት የሸሸውን አየህን (እስቲ ንገረኝ)?

33. ያን ከእምነት የሸሸውን አየህን (እስቲ ንገረኝ)?

وَأَعۡطَىٰ قَلِيلٗا وَأَكۡدَىٰٓ

34. ጥቂትን ብቻ ሰጥቶ ያቋረጠውን፤

34. ጥቂትን ብቻ ሰጥቶ ያቋረጠውን፤

أَعِندَهُۥ عِلۡمُ ٱلۡغَيۡبِ فَهُوَ يَرَىٰٓ

35, ለመሆኑ የሚያውቀው የሩቅ ሚስጢር አለውና እርሱንም ያያልን?

35, ለመሆኑ የሚያውቀው የሩቅ ሚስጢር አለውና እርሱንም ያያልን?

أَمۡ لَمۡ يُنَبَّأۡ بِمَا فِي صُحُفِ مُوسَىٰ

36. ወይስ በሙሳ ፅሁፍ ያለው አልተነገረውም?

36. ወይስ በሙሳ ፅሁፍ ያለው አልተነገረውም?

وَإِبۡرَٰهِيمَ ٱلَّذِي وَفَّىٰٓ

37. በኢብራሂም (ትእዛዛቱን) በፈፀመው ያለውስ አልተነገረዉምን?

37. በኢብራሂም (ትእዛዛቱን) በፈፀመው ያለውስ አልተነገረዉምን?

أَلَّا تَزِرُ وَازِرَةٞ وِزۡرَ أُخۡرَىٰ

38. ይኸዉም ወንጀለኛ ነፍስ የሌላውን ነፍስ ወንጀል በፍጹም አትሸከምም::

38. ይኸዉም ወንጀለኛ ነፍስ የሌላውን ነፍስ ወንጀል በፍጹም አትሸከምም::

وَأَن لَّيۡسَ لِلۡإِنسَٰنِ إِلَّا مَا سَعَىٰ

39. የሰው ልጅም የለፋበትን ብቻ እንጂ ሌላ የለዉም::

39. የሰው ልጅም የለፋበትን ብቻ እንጂ ሌላ የለዉም::

وَأَنَّ سَعۡيَهُۥ سَوۡفَ يُرَىٰ

40. የሰራውም ሁሉ ወደ ፊት ይታያል::

40. የሰራውም ሁሉ ወደ ፊት ይታያል::

ثُمَّ يُجۡزَىٰهُ ٱلۡجَزَآءَ ٱلۡأَوۡفَىٰ

41. ከዚያም ጌታው ሙሉ ምንዳውን ይመነዳዋል::

41. ከዚያም ጌታው ሙሉ ምንዳውን ይመነዳዋል::

وَأَنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ ٱلۡمُنتَهَىٰ

42. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሁሉም መጨረሻው ወደ ጌታህ ብቻ ነው::

42. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሁሉም መጨረሻው ወደ ጌታህ ብቻ ነው::

وَأَنَّهُۥ هُوَ أَضۡحَكَ وَأَبۡكَىٰ

43. እርሱ ያ ያሳቀና ያስለቀሰ ነው::

43. እርሱ ያ ያሳቀና ያስለቀሰ ነው::

وَأَنَّهُۥ هُوَ أَمَاتَ وَأَحۡيَا

44. እርሱ ያ የገደለና ሕያው ያደረገም ነው::

44. እርሱ ያ የገደለና ሕያው ያደረገም ነው::

وَأَنَّهُۥ خَلَقَ ٱلزَّوۡجَيۡنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰ

45. እርሱ ያ ጥንድን፤ ወንድንና ሴትን የፈጠረ ነው::

45. እርሱ ያ ጥንድን፤ ወንድንና ሴትን የፈጠረ ነው::

مِن نُّطۡفَةٍ إِذَا تُمۡنَىٰ

46. ይኸዉም ከፍትወት ጠብታ በማሕጸን ውስጥ በምትፈሰስ ጊዜ ነው::

46. ይኸዉም ከፍትወት ጠብታ በማሕጸን ውስጥ በምትፈሰስ ጊዜ ነው::

وَأَنَّ عَلَيۡهِ ٱلنَّشۡأَةَ ٱلۡأُخۡرَىٰ

47. ሌላውን ማስገኘትም በእርሱ ላይ ነው::

47. ሌላውን ማስገኘትም በእርሱ ላይ ነው::

وَأَنَّهُۥ هُوَ أَغۡنَىٰ وَأَقۡنَىٰ

48. እርሱ ያ ሀብትን የሰጠና ያብቃቃ ነው::

48. እርሱ ያ ሀብትን የሰጠና ያብቃቃ ነው::

وَأَنَّهُۥ هُوَ رَبُّ ٱلشِّعۡرَىٰ

49. እርሱ የሺዕራ ጌታ ነው::

49. እርሱ የሺዕራ ጌታ ነው::

وَأَنَّهُۥٓ أَهۡلَكَ عَادًا ٱلۡأُولَىٰ

50. እርሱ የቀድሞ ሰዎችን የአድ ሕዝቦችንም አጠፋ።

50. እርሱ የቀድሞ ሰዎችን የአድ ሕዝቦችንም አጠፋ።

وَثَمُودَاْ فَمَآ أَبۡقَىٰ

51. ሰሙድንም አጠፋ:: አንድንም አላስቀረም::

51. ሰሙድንም አጠፋ:: አንድንም አላስቀረም::

وَقَوۡمَ نُوحٖ مِّن قَبۡلُۖ إِنَّهُمۡ كَانُواْ هُمۡ أَظۡلَمَ وَأَطۡغَىٰ

52. በፊትም የኑህን ህዝቦች አጥፍቷል:: እነርሱ እጅግ በዳዮችና በጣም አመጸኞች ነበሩና ነው::

52. በፊትም የኑህን ህዝቦች አጥፍቷል:: እነርሱ እጅግ በዳዮችና በጣም አመጸኞች ነበሩና ነው::

وَٱلۡمُؤۡتَفِكَةَ أَهۡوَىٰ

53.የተገለበጡትንም ደፋ።

53.የተገለበጡትንም ደፋ።

فَغَشَّىٰهَا مَا غَشَّىٰ

54. ባሸፈናት ሸፈናት::

54. ባሸፈናት ሸፈናት::

فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكَ تَتَمَارَىٰ

55. (የሰው ልጅ ሆይ)፤ ከጌታህ ጸጋዎች በየትኛው ነው የምትጠራጠረው::

55. (የሰው ልጅ ሆይ)፤ ከጌታህ ጸጋዎች በየትኛው ነው የምትጠራጠረው::

هَٰذَا نَذِيرٞ مِّنَ ٱلنُّذُرِ ٱلۡأُولَىٰٓ

56. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ይህ ከቀድሞዎቹ አስጠንቃቂዎች አንዱ ነው::

56. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ይህ ከቀድሞዎቹ አስጠንቃቂዎች አንዱ ነው::

أَزِفَتِ ٱلۡأٓزِفَةُ

57. ቀራቢቱም ቀረበች::

57. ቀራቢቱም ቀረበች::

لَيۡسَ لَهَا مِن دُونِ ٱللَّهِ كَاشِفَةٌ

58. ከአላህ በስተቀር ገላጭ የላትም::

58. ከአላህ በስተቀር ገላጭ የላትም::

أَفَمِنۡ هَٰذَا ٱلۡحَدِيثِ تَعۡجَبُونَ

59. በዚህ ዘገባ ትደነቃላችሁን?

59. በዚህ ዘገባ ትደነቃላችሁን?

وَتَضۡحَكُونَ وَلَا تَبۡكُونَ

60 ትስቃላችሁን? አታለቅሱምን?

60 ትስቃላችሁን? አታለቅሱምን?

وَأَنتُمۡ سَٰمِدُونَ

61. እናንተ ዘወትር ዘንጊዎች ናችሁን?

61. እናንተ ዘወትር ዘንጊዎች ናችሁን?

فَٱسۡجُدُواْۤ لِلَّهِۤ وَٱعۡبُدُواْ۩

62. ለአላህ ስገዱ በብቸኝነትም አምልኩትም::

62. ለአላህ ስገዱ በብቸኝነትም አምልኩትም::
Footer Include